ከመጻሕፍት ዓለም (Ethio Books World)

አንዴ ስመጥሩ ነው ተብሎ ወደሚነገርለት ላውንደሪ 5 ሸሚዞች ወስጄ ሰጠሁ። ሸሚዞቹ ውድና አንዴም ያልታጠቡ ነበሩ። በቀጠሮው ቀን ስሄድ አራቱ ሸሚዞች መጥፋታቸውን ተነገረኝ። ምን እንደሚበጀኝ ብጠይቅ፣ “የማሳጠቢያው አስር እጥፍ ይከፈልሃል” ተባልኩ። 7.50 መሆኑ ነው። ሌላ ምርጫ ስለሌለኝ እሱኑ ለመቀበል ብስማማም፣ “ባለቤቱ ለጥቂት ወጣ አሉ። ጉዳዩን የምታውቀው ሰራተኛ ወልዳ ተኝታለች፣ ለጊዜው ቲኬቱን ለማግኘት አልቻልንም።” በማለት ሲያመላልሱኝ ከርመው እግሬ ስለቀጠነ ሸሚዞቼ ቀልጠው ቀሩ።

የደረቅ እጥበት ጣጣ
ከእሸቱ ተፈራ

እፍታ (መቶ ትረካዎች፥ ቅፅ አምስት) | አዘጋጅና አርታኢ ተስፋዬ ገብረአብ | 1993 ታተመ | ገጽ 422-423